ሶፎንያስ
1 በይሁዳ ንጉሥ በአምዖን+ ልጅ በኢዮስያስ+ ዘመን ወደ ሕዝቅያስ ልጅ፣ ወደ አማርያህ ልጅ፣ ወደ ጎዶልያስ ልጅ፣ ወደ ኩሺ ልጅ፣ ወደ ሶፎንያስ* የመጣው የይሖዋ ቃል ይህ ነው፦
2 “ማንኛውንም ነገር ሙሉ በሙሉ ከምድር ገጽ ጠራርጌ አጠፋለሁ” ይላል ይሖዋ።+
3 “ሰውንና እንስሳን ጠራርጌ አጠፋለሁ።
4 “በይሁዳና በኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ሁሉ ላይ
እጄን እዘረጋለሁ፤
የባአልን ቀሪዎች* ሁሉና የባዕድ አምላክ ካህናትን ስም
ከሌሎቹ ካህናት ጋር ከዚህ ስፍራ ፈጽሜ አስወግዳለሁ፤+
5 በቤት ጣሪያዎች ላይ ሆነው ለሰማያት ሠራዊት የሚሰግዱትን+
እንዲሁም በአንድ በኩል ለይሖዋ እየሰገዱና ታማኝ እንደሚሆኑ ቃል እየገቡ+
በሌላ በኩል ግን ለማልካም ታማኝ እንደሚሆኑ ቃል የሚገቡትን አጠፋለሁ፤+
6 ደግሞም ይሖዋን ከመከተል ወደኋላ የሚሉትን፣+
ይሖዋን የማይፈልጉትን ወይም እሱን የማይጠይቁትን አጠፋለሁ።”+
7 በሉዓላዊው ጌታ በይሖዋ ፊት ዝም በሉ፤ የይሖዋ ቀን ቀርቧልና።+
ይሖዋ መሥዋዕት አዘጋጅቷል፤ የጠራቸውን ቀድሷል።
8 “በይሖዋ የመሥዋዕት ቀን መኳንንቱን፣
የንጉሡን ወንዶች ልጆችና+ የባዕዳንን ልብስ የሚለብሱትን ሁሉ እቀጣለሁ።
9 በዚያም ቀን መድረኩ* ላይ የሚወጡትን ሁሉ፣
የጌቶቻቸውንም ቤት በዓመፅና በማታለል የሚሞሉትን እቀጣለሁ።
12 በዚያ ጊዜ ኢየሩሳሌምን በመብራት እፈትሻለሁ፤
ደግሞም ቸልተኛ የሆኑትንና*
በልባቸው ‘ይሖዋ መልካምም ሆነ ክፉ ነገር አያደርግም’ የሚሉትን ሰዎች እቀጣለሁ።+
13 ሀብታቸው ይዘረፋል፤ ቤቶቻቸውም ይወድማሉ።+
ቤቶችን ይሠራሉ፤ ሆኖም አይኖሩባቸውም፤
ወይንም ይተክላሉ፤ ሆኖም የወይን ጠጁን አይጠጡም።+
14 ታላቁ የይሖዋ ቀን ቅርብ ነው!+
ቅርብ ነው፤ ደግሞም በፍጥነት እየቀረበ ነው!*+
በዚያ ተዋጊው ይጮኻል።+
15 ያ ቀን የታላቅ ቁጣ ቀን፣+
የጭንቀትና የሥቃይ ቀን፣+
የአውሎ ነፋስና የጥፋት ቀን፣
የጨለማና የጭጋግ ቀን፣+
የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን ይሆናል፤+
16 በተመሸጉ ከተሞችና በቅጥር ማዕዘኖች ላይ ባሉ ረጃጅም ማማዎች ላይ+
የቀንደ መለከትና የጦርነት ሁካታ ድምፅ የሚሰማበት ቀን ይሆናል።+
ደማቸው እንደ አቧራ፣
አንጀታቸውም እንደ ፋንድያ ይፈስሳል።+
18 በይሖዋ ታላቅ ቁጣ ቀን ብራቸውም ሆነ ወርቃቸው ሊያድናቸው አይችልም፤+
መላዋ ምድር በቅንዓቱ እሳት ትበላለች፤+
ምክንያቱም በምድር ላይ የሚኖሩትን ሁሉ በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋቸዋል።”+
2 የተላለፈው ውሳኔ ከመፈጸሙ በፊት፣
ቀኑ እንደ ገለባ ከማለፉ በፊት፣
የሚነደው የይሖዋ ቁጣ ሳይመጣባችሁ፣+
የይሖዋ የቁጣ ቀን ሳይደርስባችሁ፣
3 እናንተ የጽድቅ ድንጋጌዎቹን* የምታከብሩ፣
ጽድቅን ፈልጉ፤ የዋህነትን* ፈልጉ።
ምናልባት በይሖዋ የቁጣ ቀን ትሰወሩ ይሆናል።+
4 ጋዛ የተተወች ከተማ ትሆናለችና፤
አስቀሎንም ባድማ ትሆናለች።+
5 “በባሕሩ ዳርቻ ለሚኖረው ሕዝብ ይኸውም ለከሪታውያን ብሔር ወዮለት!+
የይሖዋ ቃል በአንተ ላይ ነው።
የፍልስጤማውያን ምድር የሆንሽው ከነአን ሆይ፣ አጠፋሻለሁ፤
አንድም ነዋሪ አይተርፍም።
6 የባሕሩ ዳርቻም መሰማሪያ ይሆናል፤
ለእረኞች የውኃ ጉድጓድና ለበጎች ከድንጋይ የተሠራ ጉረኖ ይኖረዋል።
7 ከይሁዳ ቤት ለቀሩት ሰዎች መኖሪያ ስፍራ ይሆናል፤+
በዚያም የግጦሽ ቦታ ያገኛሉ።
በምሽት በአስቀሎን ቤቶች ውስጥ ይተኛሉ።
9 ስለዚህ በሕያውነቴ እምላለሁ” ይላል የእስራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ፣
“ሞዓብ እንደ ሰዶም፣+
አሞናውያንም እንደ ገሞራ ይሆናሉ፤+
ሳማ የወረሰው ምድርና የጨው ጉድጓድ ይሆናሉ፤ ለዘለቄታውም ባድማ ሆነው ይቀራሉ።+
የሕዝቤ ቀሪዎች ይዘርፏቸዋል፤
ከገዛ ብሔሬ የቀሩት ሰዎችም ይወርሷቸዋል።
10 ከኩራታቸው የተነሳ ይህ ይደርስባቸዋል፤+
ምክንያቱም በሠራዊት ጌታ በይሖዋ ሕዝብ ላይ ተሳልቀዋል፤ ራሳቸውንም ከፍ ከፍ አድርገዋል።
12 እናንተም ኢትዮጵያውያን በሰይፌ ትገደላላችሁ።+
13 እሱ እጁን ወደ ሰሜን ይዘረጋል፤ አሦርንም ያጠፋል፤
ነነዌንም ባድማና እንደ በረሃ ደረቅ ያደርጋታል።+
14 መንጎች ይኸውም ሁሉም ዓይነት የዱር እንስሳት* በውስጧ ይተኛሉ።
ሻላ* እና ጃርት በፈራረሱት ዓምዶቿ መካከል ያድራሉ።
የዝማሬ ድምፅ በመስኮት ይሰማል።
ደጃፍ ላይ ፍርስራሽ ይኖራል፤
የአርዘ ሊባኖስ እንጨቶቹ እንዲጋለጡ ያደርጋልና።
15 በልቧ ‘እኔ ብቻ ነኝ፤ ከእኔም በቀር ሌላ የለም’ ስትል የነበረችው
ያለስጋት የተቀመጠችው ኩሩዋ ከተማ ይህች ናት።
ምንኛ አስፈሪ ቦታ ሆነች!
የዱር እንስሳት የሚተኙባት ስፍራ ሆናለች።
በእሷ በኩል የሚያልፍ ሁሉ ያፏጫል፤ ራሱንም ይነቀንቃል።”+
3 ዓመፀኛ ለሆነችው፣ ለረከሰችውና ለጨቋኟ ከተማ ወዮላት!+
2 ማንንም ለመታዘዝ ፈቃደኛ አልሆነችም፤+ ምንም ዓይነት ተግሣጽ አልተቀበለችም።+
በይሖዋ አልታመነችም፤+ ወደ አምላኳም አልቀረበችም።+
3 በውስጧ ያሉት መኳንንቷ የሚያገሱ አንበሶች ናቸው።+
ፈራጆቿ የሌሊት ተኩላዎች ናቸው፤
ለጠዋት ምንም ሳያስቀሩ አጥንቱን ሁሉ ይግጣሉ።
4 ነቢያቷ እብሪተኞችና አታላዮች ናቸው።+
5 በመካከሏ ያለው ይሖዋ ጻድቅ ነው፤+ እሱ ምንም ዓይነት ስህተት አይፈጽምም።
ፍርዱን እንደማይነጥፍ የንጋት ብርሃን፣
በየማለዳው ያሳውቃል።+
ክፉ ሰው ግን ኀፍረት የሚባል ነገር አያውቅም።+
6 “ብሔራትን አጥፍቻለሁ፤ በቅጥር ማዕዘኖች ላይ ያሉ ማማዎቻቸው ወድመዋል።
ማንም ሰው እንዳያልፍባቸው መንገዶቻቸውን አፍርሻለሁ።
ከተሞቻቸው ፈራርሰዋል፤ በዚያ አንድም ሰው የለም፤ ነዋሪም አይገኝባቸውም።+
7 እኔም ‘በእርግጥ ትፈሪኛለሽ፤ ተግሣጽም* ትቀበያለሽ’ አልኩ፤+
እነሱ ግን ብልሹ ነገር ለመፈጸም ይበልጥ ጓጉ።+
8 ‘ስለዚህ ለመበዝበዝ እስከምነሳበት ቀን* ድረስ
‘ብሔራትን ለመሰብሰብ፣ መንግሥታትን ለማከማቸት፣
በእነሱም ላይ መዓቴንና የሚነደውን ቁጣዬን ሁሉ ለማውረድ የፍርድ ውሳኔ አስተላልፌአለሁና፤+
መላዋ ምድር በቅንዓቴ እሳት ትበላለች።+
10 የሚለምኑኝ ሰዎች ይኸውም የተበተኑት ሕዝቦቼ
የኢትዮጵያ ወንዞች ከሚገኙበት ስፍራ ስጦታ ያመጡልኛል።+
11 በዚያን ቀን በእኔ ላይ በማመፅ በፈጸምሻቸው ሥራዎች ሁሉ
ለኀፍረት አትዳረጊም፤+
በዚያን ጊዜ በትዕቢት ጉራ የሚነዙትን ከመካከልሽ አስወግዳለሁና፤
አንቺም ከእንግዲህ በተቀደሰው ተራራዬ ላይ ፈጽሞ አትታበዪም።+
12 እኔም ትሑት የሆነና ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ሕዝብ በመካከላችሁ እንዲቀር አደርጋለሁ፤+
እነሱም የይሖዋን ስም መጠጊያቸው ያደርጉታል።
14 የጽዮን ሴት ልጅ ሆይ፣ እልል በይ!
እስራኤል ሆይ፣ በድል አድራጊነት ጩኺ!+
የኢየሩሳሌም ሴት ልጅ ሆይ፣ በሙሉ ልብሽ ደስ ይበልሽ፤ ሐሴትም አድርጊ!+
15 ይሖዋ በአንቺ ላይ የተላለፈውን ፍርድ ሽሯል።+
ጠላትሽን ከአንቺ መልሷል።+
የእስራኤል ንጉሥ ይሖዋ በመካከልሽ ነው።+
ከእንግዲህ ወዲህ ጥፋት አያስፈራሽም።+
16 በዚያን ቀን ለኢየሩሳሌም እንዲህ ይባላል፦
“ጽዮን ሆይ፣ አትፍሪ።+
እጆችሽ አይዛሉ።
17 አምላክሽ ይሖዋ በመካከልሽ ነው።+
እንደ ኃያል ተዋጊ ያድናል።
በታላቅ ደስታ በአንቺ ሐሴት ያደርጋል።+
ለአንቺ ፍቅር በማሳየቱ ረክቶ ዝም ይላል።*
በእልልታ በአንቺ ሐሴት ያደርጋል።
ኀፍረት በተከናነቡበት ምድር ሁሉ
እንዲወደሱና ዝና* እንዲያተርፉ አደርጋቸዋለሁ።
20 በዚያን ጊዜ መልሼ አመጣችኋለሁ፤
አዎ፣ በዚያን ጊዜ እሰበስባችኋለሁ።
“ይሖዋ ሸሸገ (ተንከባከበ)” የሚል ትርጉም አለው።
ከጣዖት አምልኮ ጋር ንክኪ ያላቸውን ቁሳቁሶች ወይም ተግባሮች የሚያመለክት ሳይሆን አይቀርም።
ወይም “ርዝራዦች።”
ወይም “ደፉ።” የንጉሡን ዙፋን መድረክ የሚያመለክት ሊሆን ይችላል።
በዓሣ በር አቅራቢያ የሚገኝ ኢየሩሳሌም ውስጥ ያለ ቦታ ሳይሆን አይቀርም።
ቃል በቃል “ጸጥ ተደርገዋልና።”
ቃል በቃል “በአተላቸው ላይ የረጉትንና።” በወይን መጭመቂያ ውስጥ እንደሚሆነው ማለት ነው።
ወይም “እጅግ እየተቻኮለ ነው!”
ቃል በቃል “መራራ።”
ቃል በቃል “ፍርዶቹን።”
ወይም “ትሑታን።”
ወይም “ትሕትናን።”
ወይም “በቀትር።”
ወይም “እንክብካቤ ያደርግላቸዋልና።”
ወይም “የሚያሸብር።”
ወይም “ያመነምናቸዋልና።”
ወይም “እሱን ያመልኩታል።”
ቃል በቃል “አንድ ብሔር ያለው እንስሳ ሁሉ።”
ወይም “ገርጌሶ።” ጠፍጠፍ ያለ ረጅም መንቆር ያለው ትልቅ አሞራ።
ወይም “እርማትም።”
ወይም “እቀጣታለሁ።”
“ምሥክር ሆኜ እስከምነሳበት ቀን” ማለትም ሊሆን ይችላል።
ወይም “እኔን በትዕግሥት ጠብቁ።”
ወይም “በአንድነት እንዲያመልኩት።”
ወይም “ይግጣሉ።”
ወይም “ጸጥ ይላል፤ ያርፋል፤ ስሜቱ ይረጋጋል።”
ቃል በቃል “ስም።”
ቃል በቃል “ስም።”