ኢሳይያስ
65 “እኔን ላልጠየቁ ሰዎች ተገለጥኩ፤
ላልፈለጉኝ ሰዎች ተገኘሁ።+
ስሜን ላልጠራ ብሔር ‘እነሆኝ፤ እነሆኝ!’ አልኩ።+
2 የራሳቸውን ሐሳብ እየተከተሉ፣+
መልካም ባልሆነ መንገድ ወደሚሄዱ+
ግትር ሰዎች ቀኑን ሙሉ እጆቼን ዘረጋሁ፤+
3 እነሱ ዘወትር በፊቴ እኔን የሚያስከፋ ነገር ይፈጽማሉ፤+
በአትክልት ቦታዎች ይሠዋሉ፤+ በጡቦችም ላይ የሚጨስ መሥዋዕት ያቀርባሉ።
5 ‘እዚያው ባለህበት ሁን፤ አትጠጋኝ፤
እኔ ከአንተ ይልቅ ቅዱስ ነኝና’* ይላሉ።
እነዚህ ሰዎች በአፍንጫዬ እንዳለ ጭስ፣ ቀኑን ሙሉ እንደሚነድ እሳት ናቸው።
6 እነሆ፣ በፊቴ ተጽፏል፤
እኔ ዝም አልልም፤
ከዚህ ይልቅ እንደ ሥራቸው እከፍላቸዋለሁ፤+
ብድራቱን ሙሉ በሙሉ እመልስባቸዋለሁ፤*
7 ይህን የማደርገው እነሱ በሠሩት በደልና አባቶቻቸው በሠሩት በደል የተነሳ ነው”+ ይላል ይሖዋ።
8 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦
“አዲስ ወይን፣ በወይን ዘለላ ውስጥ ሲገኝ
አንድ ሰው ‘በውስጡ ጥሩ ነገር* ስላለ አታጥፋው’ እንደሚል፣
እኔም ለአገልጋዮቼ ስል እንዲሁ አደርጋለሁ፤
ሁሉንም አላጠፋቸውም።+
11 እናንተ ግን ይሖዋን ከተዉት፣+
ቅዱስ ተራራዬን ከረሱት፣+
መልካም ዕድል ለተባለ አምላክ ማዕድ ካሰናዱት፣
ዕጣ ለተባለም አምላክ የተደባለቀ ወይን ጠጅ በዋንጫ ከሞሉት ሰዎች መካከል ናችሁ።
12 በመሆኑም ዕጣችሁ በሰይፍ መውደቅ ይሆናል፤+
ሁላችሁም ለመታረድ ታጎነብሳላችሁ፤+
ምክንያቱም ስጣራ አልመለሳችሁም፤
ስናገር አልሰማችሁም፤+
በዓይኔ ፊት ክፉ የሆነውን ነገር ማድረጋችሁን ቀጠላችሁ፤
እኔ የማልደሰትበትንም ነገር መረጣችሁ።”+
13 ስለዚህ ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋ እንዲህ ይላል፦
“እነሆ፣ አገልጋዮቼ ይበላሉ፤ እናንተ ግን ትራባላችሁ።+
እነሆ፣ አገልጋዮቼ ይጠጣሉ፤+ እናንተ ግን ትጠማላችሁ።
እነሆ፣ አገልጋዮቼ ሐሴት ያደርጋሉ፤+ እናንተ ግን ኀፍረት ትከናነባላችሁ።+
14 እነሆ፣ አገልጋዮቼ ከልባቸው ደስታ የተነሳ እልል ይላሉ፤
እናንተ ግን ከልባችሁ ሐዘን የተነሳ ትጮኻላችሁ፤
መንፈሳችሁ ስለተሰበረም ዋይ ዋይ ትላላችሁ።
15 የተመረጡት አገልጋዮቼ ለእርግማን የሚጠቀሙበት ስም ትታችሁ ታልፋላችሁ፤
ሉዓላዊው ጌታ ይሖዋም እያንዳንዳችሁን ይገድላችኋል፤
የራሱን አገልጋዮች ግን በሌላ ስም ይጠራቸዋል፤+
16 ስለዚህ በምድር ላይ በረከትን የሚሻ ሁሉ
በእውነት አምላክ* ይባረካል፤
በምድር ላይ መሐላ የሚምልም ሁሉ
18 በመሆኑም በምፈጥረው ነገር ለዘላለም ደስ ይበላችሁ፤ ሐሴትም አድርጉ።
እነሆ፣ ኢየሩሳሌምን ለደስታ፣
ሕዝቧንም ለሐሴት እፈጥራለሁና።+
20 “ከእንግዲህ በዚያ፣ ለጥቂት ቀን ብቻ የሚኖር ሕፃንም ሆነ
ዕድሜ የማይጠግብ አረጋዊ አይኖርም።
መቶ ዓመት ሞልቶት የሚሞት ማንኛውም ሰው ገና በልጅነቱ እንደተቀጨ ይቆጠራል፤
ኃጢአተኛው መቶ ዓመት ቢሞላውም እንኳ ይረገማል።*
22 እነሱ በሠሩት ቤት ሌላ ሰው አይኖርም፤
እነሱ የተከሉትንም ሌላ ሰው አይበላውም።
የሕዝቤ ዕድሜ እንደ ዛፍ ዕድሜ ይሆናልና፤+
የመረጥኳቸው አገልጋዮቼም በእጃቸው ሥራ የተሟላ እርካታ ያገኛሉ።
24 ገና ሳይጣሩ እመልስላቸዋለሁ፤
እየተናገሩ ሳሉ እሰማቸዋለሁ።
በተቀደሰው ተራራዬ ሁሉ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳትም ሆነ ጥፋት አያደርሱም”+ ይላል ይሖዋ።